የአዲስ ጉዳይ መጽሔት ባለቤትና አዘጋጆች ተሰደዱ

August 11, 2014

ኢሳት ዜና :-በአንባቢው ማህበረሰብ ዘንድ ተቀባይነት የነበረው ሳምንታዊ መጽሔት ባለቤት እና የመጽሔቱ ሶስት
አዘጋጆች ሀገር ለቀው ተሰደዋል። የመጽሔቱ ባለቤት አቶ እንዳልካቸው ተስፋዬ ለኢሳት እንደገለጸው፤ እርሱና ጋዜጠኞቹ በስርአቱ ሲደርስባቸው የነበረውን
ወከባና አፈና ተቋቁመው የአዲስ ጉዳይ መጽሔትን ህልውና ለማስቀጠል ባደረጉት ከፍተኛ ጥረት ፤ መጽሔቱዋ በህብረተሰቡ ዘንድ ከፍ ያለ ተቀባይነት ከማግኘቷም
ባሻገር በገንዘብ አቅምም ረገድ ጥሩ ደረጃ ላይ መድረስ ችላ ነበር። አዲስ ጉዳይ እንደ አንድ ጠንካራ የፕሬስ ተቁዋም በጥሩ የእድገት ደረጃ ላይ በደረሰችበት
ወቅት በመንግስት በኩል ክሱ፣ወከባውና፣ ማስፈራሪያው እየጠነከረ መምጣቱን የገለጸው አቶ እንዳልካቸው፤ ይህም ሆኖ የህግን መስመር በጠበቀ መልኩ ሲያከናውኑ
የነበረውን ስራቸውን ለመቀጠል እስከመጨረሻዋ ሰዓት ድረስ አስፈላጊውን ጥረት ማድረጋቸውን ተናግረዋል። ሆኖም ከህግ አግባብ ውጪ እየደረሰባቸው ያለው ነገር
እንዲቆምላቸው ለሚመለከታቸው አካላት አቤቱታ ከማቅረብ ጀምሮ አስፈላጊ ናቸው የተባሉ ጥረቶችን ቢያደርጉም ተገቢውን ምላሽ ከማጣታቸውም ባሻገር ይባስ ብሎ
መንግስት በኢትዮጵያ ቴለቪዥን በይፋ በመጽሔቱ ላይ ክስ እስከመመስረት መድረሱን የአዲስ ጉዳይ መጽሄት ባለቤት ገልጿል። ክሱ ሳይደርሳቸው በመገናኛ ብዙሀን
መገለጹ ሁሉንም ሰራተኞች እንዳስገረመ የገለጸው አቶ እንዳልካቸው፤ ይህም መጪውን ምርጫ ተከትሎ መንግስት በፕሬሶችና በጋዜጠኞች ላይ ሊኖረው የሚችለው አዝማሚያ
እና ሊወስድ ያሰበው እርምጃ ምን ሊሆን እንደሚችል በግልጽ የሚያመላክት እንደሆነ ተናግሯል። ክሱ በኢቲቪ መታወጁን ተከትሎ ወከባውና ማስፈራሪያው እየከፋ
በመምጣቱም እርሱን ጨምሮ የመጽሔቱዋ ምክትል ዋና አዘጋጅ ጋዜጠኛ ኢብራሂም ሻፊ፣ ከፍተኛ አዘጋጅ ጋዜጠኛ እንዳለ ተሽ እና አዘጋጅና አምደኛ ሀብታሙ ስዩም ሀገር
ጥለው ለመሰደድ ተገደዋል። የሰንደቅ ጋዜጣ ጋዜጠኛ የሆነው ዘሪሁን ሙሉጌታም ከደህንነት ሃይሎች የሚደርስበትን ማስፈራሪያ ተከትሎ በቅርቡ አገር ጥሎ ተሰዷል።
ሕገመንግሥቱንናሕገመንግሥታዊሥርዓቱንበኃይልለመናድናሕዝቡበመንግሥትላይአመኔታእንዲያጣአድርገዋል በሚል 4 መጽሄቶችና አንድ ጋዜጣ መከሰሳቸውንመንግሥት
ማስታወቁ ይታወሳል። የብሮድካስትባለስልጣንበሰኔወር 2006 ባወጣውመረጃመሰረትፋክትበወርበአማካይ 17 ሺ 993፣አዲስጉዳይ በወር 11 ሺ 750፣ሎሚበወር
11 ሺ 250 የኮፒብዛትወይንም ከፍተኛ ስርጭትያላቸውመጽሔቶችመሆናቸውን አስታውቆአል፡፡

Leave a comment